በካናዳ ለምትኖሩ የኢትዮጵያዊያን ዳያሰፖራ አባላት

ነሀሴ 8/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዲያስፖራውን ማህበረሰብ የምክክር ሂደት ባለድርሻ አካል በማድረግ ሁሉም ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በሀገራቸው ጉዳይ አጀንዳቸውን በመስጠት በአካል ተሳትፎ እንዲያደርጉ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡

በመሆኑም በካናዳ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ኮሚሽኑ እ.ኤ.አ ከሰፕቴምበር 6/2025 ጀምሮ በካናዳ ቶሮንቶ በሚያዘጋጀው የአጀንዳ ማሰባሰብ ምክክር ምዕራፍ ላይ እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎችን በሚያስመርጥበት መርሃ-ግብር ላይ እንድትገኙ በትህትና ጋብዟችኋል፡፡

ስለሆነም በዚህ የምክክር መድረክ ላይ በግለሰብ ደረጃ ለመገኘት ከታች በተቀመጠው ሊንክ ላይ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ሀገራዊ መግባባት ሊደረግባቸው ይገባል የምትሏቸውን አጀንዳዎች ይዛችሁ በመገኘት በሂደቱ ላይ እንድትሳተፉ ኮሚሽኑ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ማሳሰቢያ፡- ኮሚሽኑ በሂደቱ በየሀገራቱ የሚኖሩ የኢትዮጵያዊያን ማህበረሰቦች ማህበር፣ የሃይማኖት ተቋማት እና የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን ለብቻ ጥሪ እያካሄደ ሲሆን ከላይ የተገለፀው እና በበይነመረብ ምዝገባ እንድታደርጉ የተጋበዛችሁት በመርሃ-ግብሩ ላይ በግለሰብ ደረጃ ለመሳተፍ የምትፈልጉትን ብቻ እንደሆነ እናሳስባለን፡፡ የስብሰባውን ቦታ የምናሳውቅ ይሆናል፡፡

To Ethiopians Diaspora Residing in Canada

The Ethiopian National Dialogue Commission is pleased to formally announce its initiative to convene a national dialogue, offering an opportunity for Ethiopian diaspora to actively participate and propose agenda items. Accordingly, the Commission will lead and coordinate an agenda collection initiative and oversee the selection of representatives for the national conference in Canada starting from September 6/2025.

The commission hereby invites all interested Ethiopian diaspora individual residing in Canada to participate the upcoming program. Moreover, registration is mandatory and can be completed through the link provided in the caption below. In this regard, participants are strongly encouraged to submit their agenda items that they consider essential for fostering national consensus and for consideration as critical national priorities.

Note:-

This invitation is exclusively intended to individuals wishing to participate in a personal capacity and does not extend to Ethiopian communities, religious institutions, or charitable organizations residing abroad. Accordingly, this call applies solely to those attending in an individual capacity. The place of the meeting will be announced.

We look forward to your active participation and valuable contributions

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSe_efAJNcp5-WVS9q1WBzhQAPfWaYSrltTU9l85vcWJDmPz-A/viewform

https://www.facebook.com/EthioNDC